አግኝ

ጥናት 10

አምልኮ:ምስጋና ለእረኛችን እግዚአብሔር

መዝሙር 23:1-6

ደረጃ 1: ታሪኩን አንብብ

የሚከተለውን ክፍል ያንብቡ ወይም ያዳምጡ

x1.0
  23:1 እግዚአብሔር እረኛዬ ነው፤
    አንዳች አይጐድልብኝም።
  2በለመለመ መስክ ያሳርፈኛል፤
    በዕረፍት ውሃ ዘንድ ይመራኛል፤
  3ነፍሴንም ይመልሳታል።
    ስለ ስሙም፣
    በጽድቅ መንገድ ይመራኛል።
  4በሞት ጥላ ሸለቆ ውስጥ፤
    ብሄድ እንኳ፣
  አንተ ከእኔ ጋር ስለ ሆንህ፣
    ክፉን አልፈራም፤
  በትርህና ምርኵዝህ፣
    እነርሱ ያጽናኑኛል።

  5ጠላቶቼ እያዩ፣
    በፊቴ ማዕድ አዘጋጀህልኝ፤
  ራሴን በዘይት ቀባህ፤
    ጽዋዬም ሞልቶ ይፈስሳል።
  6በሕይወቴ ዘመን ሁሉ፣
    በጎነትና ምሕረት በእርግጥ ይከተሉኛል፤
  እኔም በእግዚአብሔር ቤት፣
    ለዘላለም እኖራለሁ።

ደረጃ 2፡ ታሪኩን እንደገና ይናገሩ

ታሪኩን በራስዎ ቃል ለመድገም ጥቂት ጊዜ ይውሰዱ። ጮክ ብለህ መናገር ወይም መጻፍ ትፈልግ ይሆናል። ለማስታወስ እየታገልክ ከሆነ እንደገና አንብብ ወይም አድምጠው።

ደረጃ 3፡ ታሪኩን አግኝ

ታሪኩን በደንብ እንደምታውቀው ሲሰማህ ለማሰብ ጊዜ ውሰድ ወይም በሚከተሉት ጥያቄዎች ላይ ተወያዩ


Get it on Google Play
Download on the App Store

Get Discovery Bible Studies on your phone

Discover copyright ©2015-2026 discoverapp.org

መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም የቅጂ መብት © 2001 በ Biblica, Inc.® ፍቃድ የተሰጠው በ Biblica, Inc.®። መብቱ በሕግ የተጠበቀ።

Holy Bible, New Amharic Standard Version (Addisu Medebegna Tirgum) Copyright © 2001 by Biblica, Inc.® Used by permission of Biblica, Inc.® All rights reserved worldwide.